በግጭት ወቅት ስለ ወሲባዊ ጥቃት መዘገብ

የተወሰኑ የጋዜጠኝነት ተግዳሮቶች በግጭት ወቅት የተከሰቱ ወሲባዊ ጥቃቶችን ከመዘገብ በላይ ኃላፊነትን ተሸክመዋል። በጦርነት ወወቅት አስገድዶ መድፈር ጥቅም ላይ ሲውል፣ በግለሰቦች እና በማህበረሰቦች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ አለው።

ኃላፊነት የሚሰማው ጋዜተኝነት ሰዎች ሊገልፁት በቂ ቃላት ላጡት እና ለተቸገሩበት ወንጀል ትኩረት እና አንጻር ያበጅለታል። ግድየለሽነት የተሞላበት ጋዜተኝነት በተቃራኒው፣ ተጎጂዎችን ለተጨማሪ አደጋ በማጋለጥ ጭንቀት እና ውጥረት ይጨምርባቸዋል። ይህ መመሪያ የተጻፈው በተደጋጋሚ በሲአርኤቪ ጋር ተያያዥ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በሚሰሩ ጋዜጠኞች እና ፊልም ሰሪዎች ነው። መነሻውም እንደ ጋዜጠኝነት ተቋም ምርጥ ልምዶችን  ለማጋራት እና የበለጠ ለመበየን በመፈለግ ነው። ግቡም የበለጠ ትክክለኛ እና የተሻለ ግንዛቤ የታከለበት ዘገባ ፣ ታሪካቸውን የሚናገሩ ግለሰቦች ከደረሰባቸው ጥቃት በላይ የሚደርስባቸውን ጉዳት በመቀነስ ማቅረብ እንዲቻል ለማድረግ ነው።

ከመጀመርዎ በፊት ራስዎን መጠየቅ ያለብዎት ሦስት መሰረታዊ ጥያቄዎች፤
#1.
ሦስት መሰረታዊ ጥያቄዎች

ለዚህ በበቂ ሁኔታ ተዘጋጅቻለሁ?

በግጭት ቀጠና ውስጥ ስለ ወሲባዊ ጥቃት ከመገናኛ ብዙኃን ጋር መነጋገር ለማንኛውም የጥቃቱ ሰለባ የሆነች ሰው ከፍተኛ አደጋ አለው። እነዚህ መመሪያዎች አደጋው ምን እንደሆነ የተሻለ ግንዛቤ ይሰጡዎታል።
#2.
ሦስት መሰረታዊ ጥያቄዎች

ይህንን ሰው በዚህ ጊዜ እና በዚህ ቦታ ቃለ መጠይቅ ማድረግ አለብን?

የምንጮች ደህንነት መገምገም በሁሉም ደረጃ ያሉ ጋዜጠኞች ኃላፊነት ነው - በመሬት ላይ ያለው ዘጋቢ ይሁን፣ በዜና ክፍል ውስጥ ያለው አዘጋጅ እና ተመሳሳይ ዘገባ ለመስራት የሚፈልጉ ባልደረቦች።
#3.
ሦስት መሰረታዊ ጥያቄዎች

ቃለመጠይቅ የማደርግላቸው ሰዎች በመሳተፋቸው ሊደርስባቸው የሚችል መዘዝ ሙሉ በሙሉ ተረድተዋልን?

አንድ ሰው ምስክርነታቸውን እንድትጠቀሙ ወይም ምስላቸው እንዲነሳ ፈቃደና መሆናቸው ብቻ በቂ አ ይደለም። ሙሉ በሙሉ ግንዛቤ ካላገኙ በስተቀር የፈቃድ ስምምነቱ ትርጉም የለውም።
አደጋን የማያስከትሉ ሦስት አስፈላጊ አሰራሮች፤
#4.
አደጋን የማያስከትሉ ሦስት አስፈላጊ አሰራሮች

ተጎጂዎች በራሳቸው መንገድ እና በራሳቸው ጊዜ እንዲናገሩ ፍቀድላቸው

በወሲባዊ ጥቃት ጊዜ ሰዎች በአጥቂዎች እንደ ዕቃ ይቆጠራሉ - በሚደርስባቸው ነገር ላይ ቁጥጥር እንዳላቸው ግለሰቦች አይደሉም የሚቆጠሩት። ያንን ሁኔታ በመለወጥ ተጠያቂዎችን ታሪካቸውን እንዴት እንደሚናገሩ የመወሰን ዕድል መስጠት ይችላሉ?
#5.
አደጋን የማያስከትሉ ሦስት አስፈላጊ አሰራሮች

አሰቃቂነት በትውስታና እና የደህንነት ስሜት ላይ ያለው የማያቋርጥ ተጽእኖ ይረዱ

ከአሰቃቂነትን የተያያዙ ምላሾች አንዳንድ መሰረታዊ እውቀት መኖር ፈታኝ የሆኑ የቃለ መጠይቅ ሁኔታዎችን ለመወጣት እና መዘዝ የሚያስከትሉትን የዘገባ ስህተቶችን ለማስወገድ ይረዳዎታል።
አደጋን የማያስከትሉ ሦስት አስፈላጊ አሰራሮች

የእራስዎ ስሜታዊ ደህንነት እንዴት የዚሁ አካል እንደሆነ ይረዱ

#6.
ለጭካኔ መጋለጥ በሚዲያ ባለሙያዎች ላይ ስሜታዊ ጫና ይፈጥራል። እራስዎን መንከባከብ ለራስዎ - እና ለምንጮችዎ ያለዎት ግዴታ ነው።
ዘገባው ማቅረብ፤
#7.
ዘገባውን ማቅረብ

ያስታውሱ፤ ጾታዊ ጥቃት መቼም ቢሆን የታሪኩ ብቸኛ ገጽታ አይደለም።

በክስተቶች ጭካኔ ላይ ብቻ ማተኮር ምንጮቹን እና ጋዜጠኘነትን ሊጎዳ ይችላል። ለክስተቱን ጠቅላላው ሁኔታ ትኩረት ይስጡ።
#8.
ዘገባውን ማቅረብ

ምስሎቹ አይጠፉም፤ በእይታ ምርጫዎች ይጠንቀቁ

ምስሎች አንዴ ከወጡ በኋላ ሊመለሱ አይችሉም። ሁለንተናዊ የበይነመረብ መዳረሻ ሰዎችን ወደ ብዙ አይነት አደጋዎች ሊያስገባ ይችላል።